ቅዱሳት መካናት

ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በርካታ ማኅደረ ታሪክ ቅዱሳት መካናት መገኛ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱ የኦሪት መስዋዕት ሲሰዋባቸው የነበሩ ታሪካዊና እድሜ ጠገብ አድባራት፣ ውቅር፣ ፍልፍልና የዋሻ ውስጥ ቤተ መቅደሶችም አሉ፡፡ በ12ኛው ክ/ዘመን በጻድቅወንጉስ ቅዱስ ላሊበላ የተፈለፈሉትን የደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ ጣሪያው ክፍት ሆኖ ዝናብ የማያስገባው አቡነ አሮን መንክራዊ፣ ይምርሐነ ክርስቶስና ሌሎችም መካናት የሚገኙበት የተቀደሰ አካባቢ ነው፡፡
ልመናን ታክ በማድረግ በኢንዱስትሪው ዘርፍ የተሞክሮ ማዕከል የሆነው የተከዜ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ሐዋርያ ክርስቶስን ጨምሮ 21 የአንድነትና 5 በቁሪት የሚተዳደሩ ገዳማት በዚሁ አንጋፋ ሀገረ ስብከት ይገኛሉ፡፡

በእነዚህ ገዳማትም 1229 አበው መነኮሳትና 1124 እናቶች መነኮሳይያት በአጠቃላይ ከ2353 በላይ መናኞች ጤዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው በበረሀ እየኖሩ ስለዓለም ሰላም፣ ፍቅርና አንድነት እየጸለዩ የሚገኙበት ይኸው ሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ነው፡፡