የአብነት ት/ቤቶች

ዐይንና ጆሮ የሚያሻው፣ የቅዱሱ ዐይንና ጆሮ (ክፍል ሦስት)

የፕሮጀክቱ አድማስ፣ ዓላማ፣ ራእይና ግብ፣ ጥንታዊና ባሕላዊ የአብነት ትምህርት ቤት ጎጆዎችን ወደ ሰገነት በመቀየር ብቻ የተገደበ አይደለም፡፡ ደቀመዛሙርቱ መሠረታዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የሚያባክኑት ጊዜ ለንባብና ለበለጠ መራቀቅ እንዲያውሉት ማድረግን ታሳቢ ያደረገ’ንጅ፡፡ ብፁዕነታቸው ከሩቅ አሳቢ ልጆቻቸው ጋር ደቀመዛሙርቱን ተክተው እየለመኑ፣ በሔዱበት ኹሉ ለልጆቼ ብለው አስተባብረው ለክብራቸው ሳይጨነቁ አልባሳት፣ ምግብና መጠለያ እያሟሉ የደቀመዛሙርቱን እንግልት መቀነስን፣ ከእሳቸው የተሻሉ ሰዎችን ለመፍጠርም “ሀ” ብለዋል ጉዟቸውን ተያይዘውታል።

ዐይንና ጆሮ የሚያሻው፣ የቅዱሱ ዐይንና ጆሮ (ክፍል ኹለት)

ንጉሡና ካህኑ ቅዱስ ላሊበላ ያኔ የታየው ታሪክ ማስቀመጡ አልነበረም፤ ቅርስ ማውረሱም አልነበረም። ይልቁኑም የንጉሡ ዐይንና ጆሮ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ተአምራት የሠራባቸውን ቅዱሳት መካናት ለመሳለም የሚጓዘው የኢትዮጵያዊ ወገኑን የጉዞ እንግልት ማስቀረት ነበር።

ዐይንና ጆሮ የሚያሻው፣ የቅዱሱ ዐይንና ጆሮ (ክፍል አንድ)

አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ አስቸጋሪው መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ሳይበግራቸው የመንገድ መሠረተ ልማት የተሟላበትን በተሽከርካሪ፣ የመንገድ መሠረተ ልማት የሌለውን አካባቢ በባሕላዊ መጓጓዣ፣ ከፊሉን ደግሞ በእግር እየተጓዙ ሕዝባቸውን ባርከዋል፤ አስተምረዋል። አሁን ደግሞ “በቃኝ” በሚለው የሊቅነት ሚዛነ ሰብእናቸው በጸሎት ታግዘው ሰው ተክተዋል።

በፌስቡክ ያግኙን