ዐይንና ጆሮ የሚያሻው፣ የቅዱሱ ዐይንና ጆሮ (ክፍል ሦስት)
የፕሮጀክቱ አድማስ፣ ዓላማ፣ ራእይና ግብ፣ ጥንታዊና ባሕላዊ የአብነት ትምህርት ቤት ጎጆዎችን ወደ ሰገነት በመቀየር ብቻ የተገደበ አይደለም፡፡ ደቀመዛሙርቱ መሠረታዊ ፍላጎታቸውን ለማሟላት የሚያባክኑት ጊዜ ለንባብና ለበለጠ መራቀቅ እንዲያውሉት ማድረግን ታሳቢ ያደረገ’ንጅ፡፡ ብፁዕነታቸው ከሩቅ አሳቢ ልጆቻቸው ጋር ደቀመዛሙርቱን ተክተው እየለመኑ፣ በሔዱበት ኹሉ ለልጆቼ ብለው አስተባብረው ለክብራቸው ሳይጨነቁ አልባሳት፣ ምግብና መጠለያ እያሟሉ የደቀመዛሙርቱን እንግልት መቀነስን፣ ከእሳቸው የተሻሉ ሰዎችን ለመፍጠርም “ሀ” ብለዋል ጉዟቸውን ተያይዘውታል።