ዐይንና ጆሮ የሚያሻው፣ የቅዱሱ ዐይንና ጆሮ (ክፍል ኹለት)
ንጉሡና ካህኑ ቅዱስ ላሊበላ ያኔ የታየው ታሪክ ማስቀመጡ አልነበረም፤ ቅርስ ማውረሱም አልነበረም። ይልቁኑም የንጉሡ ዐይንና ጆሮ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ተአምራት የሠራባቸውን ቅዱሳት መካናት ለመሳለም የሚጓዘው የኢትዮጵያዊ ወገኑን የጉዞ እንግልት ማስቀረት ነበር።
ንጉሡና ካህኑ ቅዱስ ላሊበላ ያኔ የታየው ታሪክ ማስቀመጡ አልነበረም፤ ቅርስ ማውረሱም አልነበረም። ይልቁኑም የንጉሡ ዐይንና ጆሮ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው ተአምራት የሠራባቸውን ቅዱሳት መካናት ለመሳለም የሚጓዘው የኢትዮጵያዊ ወገኑን የጉዞ እንግልት ማስቀረት ነበር።
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በብዙ ነገር እድለኛና ባለጸጋ ነው። የእነ ቅዱስ ላሊበላ መንፈሳዊ ጸጋና የምሕንድስና ጥበብ ውጤት መገኛ ብቻ ሳይሆን፥ ምንጊዜም ጠቢባን ሰዎች ይወጡበታል፡፡ ሊቃውንትም ይፈልቁበታል፡፡
አረጋዊው አባት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ አስቸጋሪው መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥ ሳይበግራቸው የመንገድ መሠረተ ልማት የተሟላበትን በተሽከርካሪ፣ የመንገድ መሠረተ ልማት የሌለውን አካባቢ በባሕላዊ መጓጓዣ፣ ከፊሉን ደግሞ በእግር እየተጓዙ ሕዝባቸውን ባርከዋል፤ አስተምረዋል። አሁን ደግሞ “በቃኝ” በሚለው የሊቅነት ሚዛነ ሰብእናቸው በጸሎት ታግዘው ሰው ተክተዋል።