አብነት ት/ቤቶች

አብነት ትምህርት ቤቶች የቤተ ክርስቲያናችን የህልውናዋ እስትንፋሶች ናቸው፡፡

በሀገራችን የማዕከላዊ መንግሥት ምስረታ ጉልህ ሚና የነበራት ቤተ ክርስቲያናችን ፊደል ቀርጻ፣ ብራና ፍቃና ቀለም በጥብጣ ዜጎችን ያስተማረች ቀዳማዊ ትምህርት ሚኒስቴር እንደነበረች የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡

በብፁዕ_አቡነ_ኤርምያስ አስተባባሪነት በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በወልድያ ምስራቀ ፀሐይ ወይብላ ማርያም እየተገነባ ያለው መንፈሳዊ አዳሪ ትምህርት ቤት፤ በአገልጋይ እጥረት የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናት እንዲከፈቱ፣ ምዕመናንን አስተምረው ለንስሐ የሚያበቁ፣ ቀድሰው የሚያቆርቡ ማህሌታውያን በዕውቀት የተሞሉ ካህናትን ለማፍራት እና የነገዋን ቤተክርስቲያን ለማስቀጠል ዘላቂ ዓላማ ይዞ እየተገነባ ይገኛል።

ይህ የአብነት ትምህርት ቤት በ 22 ሺህ ካ.ሜ ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ 7 ሺህ ካ.ሜ የቤተክርስቲያኗ ይዞታ እና የከተማ አስተዳደሩ 15 ሺህ ካሜ በመፍቀድ ለዚህም ለተነሺ ባለ ይዞታዎች ሀገረ ስብከቱ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ካሳ በመክፈል የግንባታ ሥራው እየተካሄደ ነው፡፡

ግንባታው ሲጠናቀቅ በአንድ ጊዜ በኹሉም የጉባኤ ቤቶች 300 ወንድ እና 100 ሴት በጠቅላላ 400 ተማሪዎችን በመቀበል ሊቃውንትን የሚያፈራ ነው፡፡